Friday, May 18, 2018

የፎቶ ጋዜጠኝነት ዋጋ!!!?


አንዱ ፎቶግራፈር ባነሳው ፎቶግራፍ ተፀፅቶ ራሱን ሲያጠፋ ሌላኛው ሰው ገድሎ የሚፎክርን ግለሰብ አንስቶ በሽልማት ይንበሸበሻል-የፎቶ ጋዜጠኝነት ዋጋ!!!?
በቱርክ የ 22 ዓመት ጥቃቅን የፖሊስ መኮንን የነበረው ሜቬልት ሜትትስ Altıntaş, የሩሲያ አምባሳደር/ አንድሬ ሪክልሎቭ /ታኅሣሥ 19, 2016 ላይ የግድያ ወንጀል ፈፀመ. በጦርነት ላይ ባለስልጣኖች ከመገደላቸው በፊት ሶስት ሌሎች ሰዎችን አቁስሏል. © Burhan Ozbilici, አሶሴሽንስ ፕሬስ. የአለም ፕሬስ ፎቶ የዓመቱ እና የቦታ ዜና, የመጀመሪያ ተሸላሚ.


አንዳንዴ ጋዜጠኝነት እንደሙያ የሚጠይቃቸውን መስፈርቶች እና ሙያዊ ባህሪያት ስንከውን የህይወታችንን ውድ ዋጋ መስዋዕት በማድረግ ሊሆን እንደሚችል ምንም አይታበይም፡፡  በሙያው ክንዋኔያችን ውስጥ ምናልባትም…ትታሰራለህ/ሪያለሽ/…ትሰደዳለህ/ጃለሽ/…በጦርነት አውድማ የምትዘግብ/ቢ/ ከሆነ ህይወትህን/ሽን/ ልታጣ/ጪ/ ትችላለህ/ያለሽ/፡፡
አንዳንዴ ደግሞ በማይገመት ሰላማዊ በተባለ ቦታ መራራውን የህይወት ገፅታ መጎንጨትም ይኖራል፡፡ ለማንኛውም ስለአንዳንድ ፎቶግራፈርና ጋዜጠኛ ሙያዊ መስዋዕትነት ስናነሳ እ.አ.አ ታኅሣሥ 19, 2016 በቱርክ ውስጥ በስዕል ኤግዚቢሽን የተከሰተ ግድያ ትዝ አለኝና የፎቶግራፈሩን ድፍረን በማድነቅ፤ በአንፃሩ ደግሞ ፎቶግራፉ ለዕይታ በቅቶ ለዓለም ህዝቦች ሰላም የሚያበረክተውን አስተዋፅዖ ጥያቄ ውስጥ በማስቀረት/ለራሴ/ በብሎጋችን ለዕይታ አብቅተነዋል.ዕውን ግን ይህ ፎቶ መልካምነትንና ፍቅርን ከማስተማር ንፃሬ ታትሞ መውጣት ነበረበት/ዕውን የሚያሸልምስ ፎቶ ነው? 

 ለካርተር ሞት ያጎናፀፈውን ፎቶ …

ጋዜጠኛው ኬቨን ካርተር ልቡን በማደንደን ያነሳው ፎቶ ግራፍ የዝናን ጥግና የህይወቱን ፍፃሜ ቸረው።
1985 ላይ በሱዳን በነበረው ሁለተኛው የእርስ በርስ ጦርነት ዜጎች ለከፍተኛ ረሃብና መፈናቀል ተጋለጡ። በዚህም የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጊኤያዊ የምግብ እርዳታና መጠለያ በደቡብ ሱዳኗ አዮድ ውስጥ ያዘጋጃል።
ጋዜጠኛው ካርተር ደግሞ ወደ ደቡብ ሱዳን ያቀናል በመንገዱም ላይ ወደ መጠለያው ለመድረስ በመጓዝ ላይ ሆና ከላይ በምስሉ የምትታየው ረሃብ ያጠቃት ትንሽ ልጅ መንገድ ላይ አንገቷን ደፍታ ተቀምጣለች። ከጀርባዋ ደግሞ ጥንብ አንሳ በማረፍ በህይወትና በሞት መሃል ያለችዋን ህፃን ይጎመጃል።
ካርተር ትዕይንቱን ከአስር ሜትር ላይ ሆኖ አሞራው ደንብሮ እንዳይበር በመጠንቀቅ በካሜራው አስቀረው።
ይህ ፎቶግራፍ በኒዮርክ ታይምስ ላይ ታተመ፣ ብዙም አነጋገረ። ካርተር ለዚህ ስራው ከፍተኛውን የጋዜጠኝነት ሽልማት" Pultizer Award " አሸናፊ ሆነ። ክሶች በረቱ። ይህ ጋዜጠኛ ባሳየው -ሰብአዊነት፣ የልጅቷን ጉዳይ የተለየ ነገር የለውም በሚል ችላ ብሎ ለነፍስ አድን ሰራተኞች ባለማሳወቁ ተወገዘ።
ኒዮርክ ታይምስ በወቅቱ በልዩ እትሙ ብዙዎች የልጅቷን እጣ እንደጠየቁ ገልፀው ጥንብ አንሳው ከተባረራላት በኃላ ልጅቷ ጉዞዋን መቀጠሏንና ማገገሟን ገልፆ ወደ እርዳታ ማእከሉ ለመድረሷ ግን የሚታወቅ ነገር አለመኖሩን አስታውቆ ነበር።

ካርተርም ሽልማቱን ካገኘ ከአራት ወራት በኃላ ራሱን አጠፋ።




No comments:

Post a Comment