Friday, July 27, 2018

‹‹በኢንጂነሩ መሞት ተዳፍኖ የሚቀር ሚስጥርም ሆነ ግድብ ሊኖር አይችልም›› (አሳዬ ደርቤ)

ከቀናት በፊት የኢፌድሪ ጠቅላይ ሚኒስቴር ዶክተር አቢይ አቢይ አህመድ ሙህራንን ሰብስበው በነበረበት ወቅት ‹‹በእስካሁኑ ፍጥነታችን የምንቀጥል ከሆነ የአባይ ግድብ የዛሬ አስር ዓመትም አያልቅም›› ብለው በተናገሩ ማግስት፤ የአባይ ግድብ ስራ አስኪያጅ የሆኑት ‹ኢንጂነር ስመኛው በቀለ› መስቀል አደባባይ ላይ በጥይት ተመትተው መሞታቸውን ሰማን፡፡

Saturday, June 9, 2018

....,,,,,,,,ደጉ የአገሬ ሰው.......

በጎጃም ጠቅላይ ግዛት በባህርዳር አውራጃ መርዓዊ ዙሪያ የሚገኙ አማሮች ናቸው፡፡

እናቱ በእምቦሳነት ጥላው የሞተችበትን ጥጃ ጌታው የሆነችው እመቤት እንደ ልጇ ጡቷን አጥብታ ለወይፈንነት አድርሳዋለች፡፡

Monday, June 4, 2018

የዶ/ር አብይ ባለቤት ቀ/እ ወይዘሮ ዝናሽ ታያቸው ለካ ….

ቀዳማዊት እመቤት ወይዘሮ ዝናሽ ታያቸው ብሬ ዘገየ ለካ የደጃዝማች ብሬ ዘገየ የልጅ ልጅ ናቸው
ክቡር ደጃዝማች ብሬ ዘገየ የፋሺስት ኢጣሊያ ጦር ኢትዮጵያን በወረረበት ወቅት ብዙ የጀግንነት ገድሎችን የፈፀሙ ሰው ናቸው፡፡

Thursday, May 31, 2018

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ከአንዳርጋቸው ጽጌ ጋር ቆይታ አድርገዋል

ላለፉት 4 ዓመታት በእስር ላይ ከቆዩት እና ክሳቸው ተቋርጦ በዚህ ሳምንት ከእስር ከተለቀቁት የግንቦት 7 አመራር ከነበሩት እንዳርጋቸው ፅጌ ጋር ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ቆይታ እንደነበራቸው የሚያሳይ ምስል ፅህፈት ቤታቸው በፌስ ቡክ ገፁ የለቀቀውን ምስል እንዲህ አጋራችሁ፡፡

Sunday, May 27, 2018

ሳይነስን ለማከም 5 ቀላል መንገዶች …

በሳይነስ ለተሰቃዩ ሰዎች ይድረስ… ሼር አድርጓቸው፡፡

ሳይነስ – በሰውነታችን ውስጥ ያሉ አየር የሚንሸራሸርባቻን ክፍሎች የሚያጠቃ የህመም ዓይነት ነው፡፡

ህመሙ ሶስት ደረጃዎች ያሉት ሲሆን፣ አኪዩት፣ሰብ አኪዩት እና ክሮኒክ ሳይነስ(ሲኖሳይተስ) በመባል ይታወቃሉ፡፡

Friday, May 18, 2018

የፎቶ ጋዜጠኝነት ዋጋ!!!?


አንዱ ፎቶግራፈር ባነሳው ፎቶግራፍ ተፀፅቶ ራሱን ሲያጠፋ ሌላኛው ሰው ገድሎ የሚፎክርን ግለሰብ አንስቶ በሽልማት ይንበሸበሻል-የፎቶ ጋዜጠኝነት ዋጋ!!!?
በቱርክ የ 22 ዓመት ጥቃቅን የፖሊስ መኮንን የነበረው ሜቬልት ሜትትስ Altıntaş, የሩሲያ አምባሳደር/ አንድሬ ሪክልሎቭ /ታኅሣሥ 19, 2016 ላይ የግድያ ወንጀል ፈፀመ. በጦርነት ላይ ባለስልጣኖች ከመገደላቸው በፊት ሶስት ሌሎች ሰዎችን አቁስሏል. © Burhan Ozbilici, አሶሴሽንስ ፕሬስ. የአለም ፕሬስ ፎቶ የዓመቱ እና የቦታ ዜና, የመጀመሪያ ተሸላሚ.


Monday, May 14, 2018

በትናንቱ ተቃውሞ 55 ፍልስጤማውያን ተገድለዋል

የእስራኤል ወታደሮች 55 ለተቃውሞ አደባባይ የወጡ ሰልፈኞችን ከገደሉ ከአንድ ቀን በኋላ ፍልስጤማውያን ለተጨማሪ የተቃውሞ ሰልፍ እየተዘጋጁ ነው።
ዛሬ እስራኤል እአአ በ1948 ከተመሰረተች 70 ዓመት ታስቆጥራለች። ፍልስጤማውያን ይህን ቀን 'ናክባ' ወይም መቅሰፍት ሲሉ ይጠሩታል።
ትናንት የተገደሉት ፍልስጤማውያን የቀብር ስነ ስርዓታቸው ዛሬ ጋዛ አካባቢ የሚፈጸም ሲሆን በአካባቢው ከፍተኛ ውጥረት ይነግሳል ተብሎ ይጠበቃል።

Sunday, May 13, 2018

በጀርመን ቡንደስሊጋ ሀምበርግ እግርኳስ ክለብ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ ሁለተኛው ዲቪዚዮንን ተቀላቀለ፡፡


በጀርመን ሀምበርግ እግርኳስ ክለብ ቡንደስሊጋው ከተጀመረ ከ1963 እ.አ.አ ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ ሁለተኛ ዲቪዚዮንን ተቀላቀለ፡፡
ሀምበርግ እግርኳስ ክለብ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ ከቡንደስሊጋ ወረደ

የመጨረሻ ጨዋታቸውም ደጋፊዎች ወደሜዳ በወረወሩት ቀይ ነበልባል እና ከተቃራኒ ቡድን ጋር በፈጠሩት ግርግር 15 ቂቃዎች እየቀሩት ተጠናቋል፡፡ 

Saturday, May 12, 2018

ኮከቦቹ ስለ ሮናልዲኒሆ ጎቾ ምን አሉ?


ስለ ራሱ #ሮናልዲኒሆ
ፈጣሪ ለሁሉም ፍጡር ስጦታ ሰጥቷል አንዳንዱ እንዲፅፍ አንዳንዱ እንዲደንስ አንዳንዱ ደግሞ የሰው ልጆችን የማዳን ጥበብ እኔ ደግሞ እግር ኳስ እንድጫወት ተሰጥቶኛል ከነዛ ከስጦታዎች ሁሉ የላቀው ስጦታ ለኔ ፈጣሪ ሰጠኝ!!!





#ዲያጎ_ማራዶና ለእኔ ሮናልዲኒሆ በእግር ኳስ ታሪክ ትልቁ ምልክት ነው። እንደሚመስለኝ በእኔ አመለካከት 2003 – 2005 የነበረው ሮናልዲኒሆ  ሊዬ ሜሲ እና ሲአር 7/CR7/ እጅግ በጣም የገዘፈ ተጫዋች ነበር በእረግጥ CR7 እና Messi ብዙ ጎሎችን ስላስቆጠሩ

Thursday, May 10, 2018

የንስር አሞራ ሚስጥራዊ ተፈጥሮ

ፍጥረታት ሁሉ ይችን ምድር ሲወርሱ የተሰጣቸው አስገራሚና ልዩ ውብ ተፈጥሮ አላቸው፡፡ ከነዚህ የተፈጥሮ ፀጋ ከተሰጣቸው ድንቅ የምድራችን ፍጥረታት መካከል አንዱ የንስር አሞራ ነው፡፡ የንስር አሞራ ምድቡ ከአእዋፍ ወገን ሲሆን ተፈጥሮ የሰጠችው ድንቅ ሚስጥራዊ ተፈጥሮ ግን የተለየ ያደርገዋል፡፡
                                                                                                                     ፎቶ:ከኢንተርኔት
 ዛሬ በዓለማችን የሰው ልጆች አማካኝ የዕድሜ ጣሪያ 65 ዓመት በሆነበት ዘመን ንስር አሞራ ከአዕዋፋት ዘር 70 ዓመት የመኖር ፀጋ ተፈጥሮ የቸረችው የእድሜ ባለጸጋ ነዉ። አስገራሚው ነገር ይህ ድንቅ አእዋፍ ዕድሜው 40 ሲሆን ተፈጥሮ ሁለት አማራጮችን በፊቱ ታቀርብለታለች፤ እንደ አማረበት መሞት ወይም እድሜውን  ወደ 70 አመት ከፍ ለማድረግ ተፈጥሮ ያዘጋጀችለትን የመከራና የስቃይ ጽዋ ምሬት አጣፍጦ በመጎንጨት ተጨማሪ የ30 ዓመት የድል ዋንጫ መቀዳጀት፡፡

Thursday, April 26, 2018

West Africa Gorillas Still Endangered And In Dire Need Of Protection – Report

Gorillas and chimpanzees may be twice as numerous in West Africa as previously thought, but the apes are still endangered, declining fast and in dire need of protection, an international study found Wednesday.
Gorillas,photo from internet
Prior estimates were based on nest counts taken from isolated areas across the great apes’ habitat range, said the report in the journal Science Advances.


Wednesday, April 25, 2018

በስፔን 90 ኩንታል ኮኬይን ተያዘ

በስፔን አልጀሲራስ ወደብ ሪከርድ በሆነ መጠን 90 ኩንታል የኮኬይን ዕፅ መያዙን የጉምሩክ ኃላፊዎች አስታወቁ፡፡
ኮኬይን እየሸጋገረ የነበረው ትልቅ ኮንቴነር የጫነ መርከብ ሲሆን፥ በሙዝ መያዣ ሳጥኖች ውስጥ ተደብቆ እንደነበረ ተገልጿል፡፡
ኮንቴይነሩን የያዘው መርከብ የተነሳው ከደቡብ አሜሪካዋ ኮሎምቢያ ቱርቦ ወደብ ነው ተብሏል፡፡
ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ እስከአሁን ሁለት ግለሰቦች ከፈረንሳይ አራት ደግሞ ከስፔን ተይዘዋል በጥቅሉ ስድስት ሰዎች መያዛቸውን ፖሊስ አስታውቋል፡፡

የቫይታሚን ዲ እጥረት እና የስኳር በሽታ ተጋላጭነት

ባሳለፍነው ሳምንት የተሰራ አዲስ ጥናት የቫይታሚን ዲ እጥረት ያለባቸው ሰዎች ለስኳር በሽታ የመጋለጥ አድላቸው ከፍተኛ መሆኑን አመልክቷል።
በአሜሪካ ካሊፎርኒያ ዩኒቨርሲቲ ሳንዲያጎ የጤና ኮሌጅ የተካሄደው ጥናቱ ለስኳር በሽታ ያልተጋለጡ እና በስኳር በሽታ የተያዙ አዋቂዎችን ተመልክቷል።


በጥናቱ ላይም 903 ሰዎች የተካፈሉ ሲሆን፥ ለ10 ዓመታት ገደማ ክትትል ከተደረገባቸው በኋላ የተገኘው ውጤት ከሰሞኑ ይፋ ተደርጓል።
በዚህ ወቅትም የተሳታፊዎቹ “25-ሀይድሮክሲ ቫይታሚን” የሚባለው የቫይታሚን ዲ አይነት መጠን የተለካ ሲሆን፥ አጠቃላይ የጤናቸው ሁኔታም ክትትል ተደርጎበታል።