Friday, July 27, 2018

‹‹በኢንጂነሩ መሞት ተዳፍኖ የሚቀር ሚስጥርም ሆነ ግድብ ሊኖር አይችልም›› (አሳዬ ደርቤ)

ከቀናት በፊት የኢፌድሪ ጠቅላይ ሚኒስቴር ዶክተር አቢይ አቢይ አህመድ ሙህራንን ሰብስበው በነበረበት ወቅት ‹‹በእስካሁኑ ፍጥነታችን የምንቀጥል ከሆነ የአባይ ግድብ የዛሬ አስር ዓመትም አያልቅም›› ብለው በተናገሩ ማግስት፤ የአባይ ግድብ ስራ አስኪያጅ የሆኑት ‹ኢንጂነር ስመኛው በቀለ› መስቀል አደባባይ ላይ በጥይት ተመትተው መሞታቸውን ሰማን፡፡